Return to BahaiPrayers.net
Facebook
ጌታ አምላኬ ሆይ አንተ የተከበርክ ነህ! ለእኔና የአንተን ገጽ ለማየት ለፈለጉት ሁሉ ከቸርነትህና በረከት ከተመላበት ፀጋህ መስጠቱ የሚጠበቀውን ከስጦታዎችህና ከችሮታዎችህ መለገሱም ተገቢ የሆነውን እንድትልክልን በኃይል በሚነፍሱት የፀጋህ ነፋሶች በእነዚያም በዓላማህ ንጋቶችና በመንፈሳዊ የእውቀት ብልጭታህ የንጋት ሥፍራዎች በሆኑት እማፀንሃለሁ፡፡ ጌታዬ ሆይ÷ እኔ ምስኪንና ጉስቁል ነኝ! በሀብትህ ውቅያኖስ ውስጥ አስጥመኝ፣ የተጠማሁ ነኝ ከፍቅራዊ ደግነትህ የህይወት ውሃዎች እንድጠጣ አድርገኝ፤
አገልጋችህን ፀጋ በተመላበት አምላካዊ ጥበቃህ ዛፍ ጥላ ሥር በአንድ ላይ እንድትሰበስባቸው÷ በአንተው በራስህና በእርሱ የአንተ የራስህ ህልውና ክስተትና በሰማይና በምድር ለሚገኙት ሁሉ ክፉውን ከበጎ የሚለይ ቃልህ አድርገህ በሰየምከው እማፀንሃለሁ፡፡ ከፍሬዎቹ እንዲሳተፉ ÷ወደቅጠሎቹ መንኮሻኮሽ÷ከቅርንጫፎቹ ላይ ወደሚያዜመውም ወፍ ድምጽ ጣፋጭነት ጆሮዎቻቸውን እንዲያቀኑ እርዳቸው፡፡ በእውነቱ÷ አንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ÷ የማይደረስበቱ÷ ፍጹም ኃያሉ÷ ከሁሉም በላይ ፀጋ የተመላው ነህና፤
አቤቱ አንተ መሐሪው አምላክ ሆይ! አቤቱ አንተ ኃያልና ሃይል የተመላው ሆይ! አቤቱ አንተ ከሁሉም በላይ ለጋስ አባት ሆይ! እነዚህ አገልጋዮች ወደ አንተ ተመልሰው በአንተ ደጀሰላም ለመማፀን÷ ከአንተ ታላቅ መተማመኛ የአንተን የማያልቁ በረከቶች ለመለመን በአንድ ላይ ተሰባስበዋል፡፡ እነርሱ ከአንተ መልካም ደስታ በስተቀር ሌላ ዓላማ የላቸውም፡፡ የሰውን ዘር ዓለም ከማገልገል በስተቀር ሌላ ዕቅድ የላቸውም፡፡
አምላክ ሆይ! ይህን ስብሰባ ብሩህ አድርገው ልቦችን መሐሪዎች አድርጋቸው፡፡ የቅዱስ መንፈስን በረከቶች አውርድላቸው፤ የመንግስተ ሰማይ ኃይል አጎናጽፋቸው፣የመንግስተ ሰማይ አእምሮዎች በመስጠት ባርካቸው፤ በሙሉ ትሕትናና ፀፀት በተመላበት ልብ ወደ አንተ መንግስት በመመለስና ለሰው ዘር ዓለም አገልግሎት በመስጠት ሥራ እንዲጠመዱ ቅንነታቸውን አብዛ፡፡ እያንዳንዱ ብሩህ ሻማ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ አንፀባራቂ ኮከብ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ በአምላክ መንግስት ውስጥ ውበት የተመላ ቀለምና አስደሳች መዓዛ ያለው ይሁን፡፡
አቤቱ አንተ ለጋስ አባት ሆይ !ቡራኬዎችህን አጎናጽፈን፣ ጉድለቶቻችንን አትመልከት፡፡ በጥበቃህ መጠለያ ሥር ጠልለን፡፡ ኃጢአቶቻችንን አትመልከት፡፡ በምሕረትህ ፈውሰን እኛ ደካሞች ነን አንተ ግን ኃያል ነህ፡፡ እኛ ምስኪኖች ነንሀ አንተ ግን ሀብታም ነህ፡፡ እኛ ሕሙማን ነን፤አንተ ደግሞ ሐኪም ነህ፡፡ እኛ ችግረኞች ነን አንተ ግን ከሁሉ በላይ ቸር ነህ፡፡
አምላክ ሆይ! ሀብትህን አጎናጽፈን፡፡ አንተ ኃይል የተመላው ነህ፡፡ አንተ ሰጪው ነህ አንተ ለጋሱ ነህ፡፡
- Bahá'u'lláh