Return to BahaiPrayers.net
Facebook
ሟች ወንድ ከሆነ፤
አምላኬ ሆይ ! ይህ በአንተና በምልክቶችህ ያመነ ከአንተ በቀር ከሁሉም ሙሉ በሙሉ የተላቀቀና ፊቱን ወደ አንተ የመለሰ አገልጋይህና የአገልጋይህምልጅ ነው፡፡ አንተ በእውነቱ ምሕረትን ከሚያደርጉት ሁሉ በላይ መሐሪው ነህ፡፡
አቤቱ አንተ የሰዎችን ኃጢአት ቅር የምትልና ስሕተቶቻቸውን የምትሸፍን አምላክ ሆይ፣ከቸርነትህ ሰማይና ከፀጋህ ውቅያኖስ የሚጠበቀውን አድርግለት ከምድርና ከሰማይ መፈጠር በፊት ጀምሮ ወደነበረው የላቀ ምሕረትህ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዲገባ ፈቃድህ ይሁን፡፡ ከአንተ ከዘለዓለም ይቅር ባዩ ከሁሉም በላይ ለጋሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለምና፡፡
ሟች ሴት ከሆነች
አምላኬ ሆይ! ይህቺ በአንተና በምልክቶችህ ያመነች፣ ከአንተ በቀር ከሁሉም ሙሉ በሙሉ የተላቀቀችና ፊቷን ወደ አንተ የመለሰች ሴት አገልጋይህና የሴት አገልጋይህም ልጅ ናት፡፡ አንተ በእውነቱ ምሕረትን ከሚያደርጉት ሁሉ በላይ መሐሪው ነህ፤
አቤቱ አንተ የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የምትልና ስሕተቶቻቸውን የምትሸፍን አምላክ ሆይ ከቸርነትህ ሰማይና ከፀጋህ ውቅያኖስ የሚጠበቀውን አድርግላት፤ ከምድርና ከሰማይ መፈጠር በፊት ጀምሮ ወደነበረው የላቀ ምህረትህ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንድትገባ ፈቃድህ ይሁን፤ ከአንተ ከዘላለም ይቅር-ባዩ ከሁሉም በላይ ለጋሱ በስተቀር ለተላ አምላክ የለምና፤
ከሁለቱ ፀሎቶች ለሟች ፆታ የሚስማማውን ይድገም፡፡ ከዚህም በኋላ አላህ ኡ አብሃ የሚለውን ሰላም ከሚከተሉት ስድስት ትቅሶች ከእያንዳንዳቸው በፊት አንዳንድ ጊዜ ማለትም(በድምሩ ስድስት ጊዜ) በመድገም ጥቅሶቹን እያንዳንዳቸውን አሥራ ዘጠኝ ጊዜ በሚከተለው ቅደም ተከተል ይድገም፡፡
አላህ-ኡ-አብሃ (አንድ ጊዜ)
በእውነቱ፡ ሁላችንም እግዚአብሔርን
እናመልካለን፡፡ (19 ጊዜ)
አላህ-ኡ አብሃ (አንድ ጊዜ)
በእውነቱ ሁላችንም በእግዚአብሔር ፊት
እንሰግዳለን፡፡ (19 ጊዜ)
አላህ-ኡ- አብሃ (አንድ ጊዜ)
በእውነቱ፡ ሁላችንም ህይወታችንን ለአምላክ
ሰጥተናል፡(19 ጊዜ)
አላህ-ኡ-አብሃ(አንድ ጊዜ)
በእውነቱ ፡ ሁላችንም አምላክን እናወድሳለን፡፡
(19ጊዜ)
አላህ-ኡ-አብሃ(አንድ ጊዜ)
በእውነቱ፣ ሁላችንም ለእግዚአብሔር ምስጋና
እናቀርባለን፡፡(19 ጊዜ)
አላህ-ኡ-አብሃ (አንድ ጊዜ)
በእውነቱ፡ ሁላችንም በአምላክ እንታገሣለን፡፡
(19 ጊዜ)
- Bahá'u'lláh