Return to BahaiPrayers.net
Facebook
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ÷ በፀጋህና በቸርነትህ ኃዘኔን አጥፋ በሉዓላዊነትህና በኃይልነትህ ሥቃዬን አስወግድ፣ አምላኬ ሆይ÷ ኃዘን ከየአቅጣጫው በከበበኝ ጊዜ ፊቴን ወደ አንተ ሳቀና ትመለከተኛለህ፡፡ አቤቱ አንተ የፍጡራን ሁሉ ጌታ፣ ለሚታዩና ለማይታዩት ነገሮች ሁሉ ጥላና ከለላ የሆንከው ሆይ! ከእነዚያ ፎቶቻችውን ወደ አንተ ከመመለስ ከቶ ምንም ከማያግዳቸው ጋር ትቆጥረኝ ዘንድ÷ የሰዎችን ልቦችና ነፍሶች በገዛው ስምህ÷ በምሕረትህ ውቅያኖስ ማዕበልና በፀጋህ የቀኑ ኮከብ ድምቀት እማጠንሃለሁ፡፡
ጌታዬ ሆይ÷ በቀናትህ የደረሰብኝን አንተ ትመለከታለህ፡፡ አንተን ለማገልገል ለመነሣትና ባህርያትህን ለማሞገስ የሚያስችለኝ ታዝልኝ ዘንድ በእርሱ የስሞችህ ጎሕና የባህርያትም የንጋት ሥፍራ በሆነው እማጠንሃለሁ፡፡ አንተ በእውነቱ ፍጹም ኃያሉ÷ ከሁሉም በላይ ኃይል የተመላው፣የሰዎችን ሁሉ ፀሎት ሰሚው ነህና፡፡
በመጨረሻም ተግባሬን ሁሉ ትባርክልኝ ከኃጢአቴም ታነፃኝ ፍላጎቴንም ታሟላልኝ ዘንድ በገጽህ ብርሃን እለምንሃለሁ፡፡ አንተ ለስልጣንህና ለገዥነትህ እያንዳንዱ አንደበት የመሰከረልህ እያንዳንዱ የሚገነዘብ ልብ ስለ ግርማህና ስለ ሉዓላዊነትህ ያወቀልህ ነህና፡፡ የጠየቁህን ከምትሰማው መልስም ለመስጠት ከማትቆጠበው ከአንተ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡
ከእግዚአብሔር በስተቀር ችግርን የሚያስወግድ አለ ወይ? በል፡- ለእግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው! እርሱ አምላክ ነው! ሁሉም አገልጋዮቹ ናቸው፡ ሁሉም በትዕዛዙ ይኖራሉ፤
አቤቱ አንተ በመከራዬ ጊዜ ማረፊያዬ! በጭንቀቴም ጊዜ ጋሻዬና መከታዬ፣ በችግር ጊዜ መጠጊያዬና መሸሻዬ! በብቸኝነቴም ጊዜ ባልደረባዬ! በኃዘኔ ጊዜ መጽናኛዬ! በጓደኛ -ቢነቴም ጊዜ አፍቃሪ ጓደኛዬ! የኃዘኔን ሥቃይ የምርቃት ኃጢአቴንም ይቅር የምትል ጌታ አምላኬ ሆይ!
በዚህ በመለኮታዊ አንድነትህ ዘመን የአንተን ፈቃድ ከሚቃወም ነገር ሁሉ እንድትከልለኝ እንከን የሌለብኝና ያልተበከልኩ ሆኜ ፀጋህን ዛፍ ጥላ እንዳልፈልግ እንቅፋት ከሚሆንብኝ ርኩሰት ሁሉ እንድታነፃኝ፣ ሙሉ በሙሉ ወደ አንተ በመዞር በሙሉ ልቤ አዕምሮዬና አንደበቴ በጋለ ስሜት እማፀንሃለሁ፡፡
ጌታ ሆይ በደካማው ላይ ምሕረት ይኑርህ፤ በሽተኛውንም ፈውስ፣ የሚያቃጥለውንም ጥም አርካ፡፡ የፍቅርህ እሳት የሚጋጋበትን ልብ ደስ አሰኘው፣በመንግስተ ሰማያዊ ፍቅርህና መንፈስህ ነበልባል አንድደው፡፡
የመለኮታዊ አንድነት መቅደሶችን በቅድስና ካባ አጎናጽፋቸው ፣የቸርነትህንም ዘውድ በራሴ ላይ ድፋልኝ፡፡
ፊቴን በፀጋህ ሉል ብርሃን አብራልኝ፣ በቅድስናህም ደጀሰላም አገልግሎት ዘንድ በቸርነትህ እርዳኝ፡፡
ልቤ ለፍጡራንህ በሚኖረው ፍቅር እንዲጥለቀለቅ አድርገው፣የምህረትህ ምልክት፣ የፀጋህ መታወቂያ፣በተወዳጆችህ መካከል ስምምነት አስፋፊ፣ ለአንተ ያደርኩ፣ ያንተን ትዝታ የማወሳ፣ ራሴንም ረስቼ ያንተ የሆነውን ሁሉ የማስታወስ እንድሆን ፈቃድህ ይሁን፡፡
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣ የይቅርታህንና የፀጋህን ልዝብ ነፋስ አታርቅብኝ፣ ከረዳትነትህና ከፍቅርህ ምንጭ አትንሳኝ፤ በጠባቂ ክንፎችህ ጥላ ሥራ እንዳርፍ ፍቀድልኝ፣ የፍጹም ጠባቂ አይንህን እይታ አሳርፍብኝ፡፡
ስምህን በሕዝብህ መካከል እንዳወድስ፣ ድምጼም በታላላቅ ጉባኤዎች ላይ ከፍ እንዲል፣ ከከናፍሮቼም የአንተ ምስጋና ጎርፍ እንዲፈስ ምላሴን አፍታታ፡፡ አንተ በእውነቱ፣ ፀጋ-የተመላው የተመሰገነው፣ ኃያሉ፣ ምንም የማይሳነው ነህና!
ጌታዬ ተወዳጄ፣ ፍላጎቴ ሆይ! በብቸኝነቴ ጊዜ ተጎዳኘኝ በግዞቴም ጊዜ አብረኽት ሁን፤ ኃዘኔን አስወግድልኝ፣ ለውበትህም ያደርኩ አድርገኝ፣ ከአንተ በስተቀር ከሌላው ነገር ሁሉ አግልለኝ፣ በቅድስናህም መዓዛ ወደ አንተ ሳበኝ፡፡ በመንግስትህም ውስጥ ውሎዬን ከእነዚያ ከአንተ በስተቀር ከሌላው ነገር ሁሉ ከተላቀቁት፤ የአንተንም ቅዱስ ደጀሰላም ለማገልገል ከሚናፍቁትና በእምነትህ ከፀኑት ጋር እንድጎዳኝ አድርገኝ፤ ለመልካም ፈቃድህ ከበቁት ሴት አገልጋዮችህ አንዷ ለመሆን አስችለኝ፡፡ በእውነቱ አንተ ፀጋ የተመላው ለጋሱ ነህና፡፡
- Bahá'u'lláh