Return to BahaiPrayers.net
Facebook
አምላኬ ሆይ! አምላኬ ሆይ! የአገልጋዮችህን ልብ አስተባብር፤ ታላቁን ዓላማህንም ግለጽላቸው፤ ትዕዛዝህን ይከተሉ፣ በሕግህም ይኖሩ ዘንድ፣ አምላክ ሆይ በጥረታቸው እርዳታቸው ለአንተም እንዲያገለግሉ ኃይልን ስጣቸው፣ አምላክ ሆይ! ራሳቸውን ለራሳቸው አትተው፤ እርምጃቸውን ሁሉ በዕውቀት ብርሃን ምራው፣ በፍቅርህም ልቦቻቸው አስደስት፡፡ በእውነቱ አንተ ረዳታቸውና ጌታቸው ነህና፡፡
የአንድነት ብርሃን መላዋን ዓለም እንዲያለብሱና “መንግስት የአምላክ ናት ” የሚለውም ማኅተም በሕዝቦቿ ሁሉ ግንባር ላይ እንዲታተም የአምላክ ፈቃድ ይሁን፡፡
አምላክ ሆይ! አምላኬ ሆይ! በእውነቱ ምህረቶችህ ሁሉ በእነዚህ ነፍሶች ላይ እንዲወርዱ አንተን በመጠየቅ እለምንሃለሁ፡፡ በደጀ ሰላምህ ፊት ሆኜ እማፀንሃለሁ፣ ለችሮታህና ለእውነትህ ምረጣቸው፡
ጌታ ሆይ! ልቦችን በማስተባበር አስተሳስራቸው፣ ነፍሶችን ሁሉ በስምምነት አጣምራቸው፣ መንፈሶችንም በቅዱስነትህና በአንድነትህ ምልክቶች አስደስታቸው፤ ጌታ ሆይ! እነዚህን ፊቶች በአንድነት ብርሃን አማካይነት ብሩህ አድርጋቸው፡፡ ለመንግስትህ እንዲያገለግሉ የአገልጋዮችህን ሽንጦች አጠንክርላቸው፡፡
አቤቱ አንተ ወሰን የሌለው ምሕረት ባለቤት የሆንከው ጌታ ሆይ! አቤቱ የኃጢአት ስርየትና የይቅርታ ጌታ ሆይ! ኃጢአቶቻችንን አስተሰርይልን ስለጉድለቶቻችንም ይቅርታ አድርግልን፣ ወደ ኃያልነትና ወደ ሥልጣን መንግስት በመፀለይ በመንበርህ ቅርበት ትሑታን፣ በማስረጃዎችህም ክብር ፊት ታዛዦች በመሆን ወደ ምህረትህ መንግሥት ፊቶቻችንን እንድንመልስ አድርገን፡፡
አቤቱ ጌታ አምላክ ሆይ! በፍቅርህ በረከት እንደ ባህር ማዕበሎች እንደ አትክልት ሥፍራ አበቦች የተባበርንና የተስማማን እንድንሆን አድርገን፡፡ ጌታ ሆይ! በአንድነትህ ምልክቶች አማካይነት ልቦችን አስፋቸው፣ የሰው ዘርንም ሁሉ ከአንድ አይነት የክብር ከፍታ እንደሚያበሩ ከዋክብት፣ በሕይወት ዛፍህ ላይ እንደሚያድጉ ፍጹማን ፍሬዎች አድርጋቸው፡፡
በእውነቱ፣ አንተ ፍጹም ኃይሉ፣ በገዛ ራሱ ነዋሪ፣ ሰጪው ይቅር ባዩ መሐሪው ሁሉን አዋቂው አንድዬው ፈጣሪ ነህና፡፡
- Bahá'u'lláh