Return to BahaiPrayers.net
Facebook
Assemblies
ፍጹም ኃይል የተመላው በፀጋው የላቀ ድል ለማግኘት እንድትችሉ ይረዳችሁ ዘንድ ወደ መንፈሳዊ ጉባኤው ክፍል በምትገቡበት ጊዜ፣ በእግዚአብሔር ፍቅር በሚርገበገብ ልብና እርሱን ከማስታወስ በቀር ከሌላ ነገር ሁሉ በነፃ አንደበት ይሁን ፀሎት አድርጉ፡፡
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ! እኛ በዚህ ታላቅ ቀን ከአንተ በቀር ከሁሉም ተላቅቀን ወደ ቅዱስ ገጽህ በፍቅር የተመለስን አገልጋዮችህ ነን፡፡ በሰው ዘር መካከል ቃልህን ከፍ ለማድረግ ባለን የዓላማ ስምምነት በአመለካከታችንና በአስተሳሰባችን ተዋሕደን በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሰብስበናል፡፡ ጌታ አምላካችን ሆይ! የአንተ መለኮታዊ መርሖ ምልክቶች፣ በሰዎችም መካከል የላቀው እምነትህ ሰንደቅ ዓላማዎች፣ ለኃይሉ ቃል ኪዳንህም አገልጋዮች እንድንሆን አንተ ከሁሉም የላቅህ ጌታችን ሆይ በአብሀ መንግስትህን የመለኮታዊ አንድነትህ መገለጫዎች፣ በሁሉም አካባቢዎች ላይ የሚያበሩ አንፀባራቂ ከዋክብትም አድርገን፡፡ ጌታ ሆይ! በአስገራሚው ፀጋህ ሞገድ የሚንቀሳቀሱ ባሕሮች ፍፁም ክብር ከተመሉት ከፍታዎች የሚጎርፉ ጅረቶች፣ በመንግስጠ ሰማያዊው እምነት ዛፍ ላይ ያሉ መልካም ፍሬዎችና በመለኮታዊ የወይን እርሻህ ውስጥ በፀጋህ ልዝብ ነፋሶች የሚወዛወዙ ዛፎች እንድንሆን እርዳን፤ አምላክ ሆይ! አስተሳሰቦቻችን አመለካከቶቻችንና ስሜቶቻችን ልክ የአንድነት መንፈስ ይገልፁ ዘንድ ልክ እንደ አንድ ባህር ሰንበሮች አንድ እንድንሆንና እንደ አንፀባራቂው ብርሃንህ ጨረሮች በአንድነት እንድንጣመር፣ ነፍሶቻችን ለመለኮታዊ አንድነትህ ጥቅሶች እንዲገዙ ልቦቻችንም በጸጋህ ጎርፎች እንዲደሰቱ አድርጋቸው፡፡ አንተ ፀጋ የተመላው ለጋሱ ሰጪው ፍጹም ኃያሉ መሐሪው ሩኅሩህ ነህና፡፡
አቤቱ አንተ ሩኅሩህ አምላክ ሆይ! በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ በታላቅ ትሕትና በአንድ ላይ ተሰባስበናል፡፡ አንድ እንድንሆንና እንድንስማማ፣ እርስ በርሳችንም እንድማርና ወተት በጣፈጠ ግንኙነት እንድንቀራረብ፣ ለሰውም ዘር አንድነት መንግስት ምጹዓት ምክንያት እንድንሆን ፊቶቻችንን ወደ አንተ መንግስት በመመለስ ማረጋገጫህንና እርዳታህን እንለምናለን፡፡ ምኖታችን እንዲፈፀምልን በንፁህ ልብና በብሩህ መንፈስ ወደ አንተ እንድንፀልይና እንድንለምንህ እርዳን፡፡
ፍጹም ኃያሉ ሆይ! በፀጋህና በቸርነትህ ተመልክተን እንጂ ኃጢአታችንን አትመልከት፡፡ ጉድለቶቻችንን ይቅር በለን፡፡ በረከትህን አውርድልን፡፡ የፍቅርህን እሳት አቀጣጥለህ የአጉል ምልኮን የስሜትንና የምኖትንን ግርዶሽ አቃጥለህ አጥፋቸው ከእኔነት ድክመት ተከላክለህ ጠብቀን በመሐሪነትህ ዛፍ ጥላ ሥር ከልለን፣ የመንፈስንም ፀጥታና ዕረፍት ስጠን፡፡
በእውነቱ አንተ ኃይል የተመላው ፣ኃያሉ ነህና፡፡
በመንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ መዝጊያ ላይ የሚደረግ ፀሎት
አምላክ ሆይ! አምላክ ሆይ! እኛ በአንተ አምነን፣ኪዳንህና በአዲሱ ሥርዓትህ ፀንተን፣ ወደ አንተ ተስበን፣ በፍቅርህ እሳት ተቀጣጥለን፣ የእምነትህም ቅን እማኖች ሆነን በዚህ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ተሰባስበን መገኘታችንን ከማይታየው የአንድነትህ መንግስት ተመልከተን፤ እና በአንተ የወይን እርሻ ውስጥ በማገልገል ላይ የምንገኝ፣ ሃይማኖትህን አስፋፊዎች ራሳችንን ለአንተ አገልግሎት የሰጠን የአንተ ገጽታ አምላኪዎች ለተወዳጆችህ ትሁታን፣ በበርህም ፊት ታዛዦች የሆንን፣ ሕሩያንህን በማገልገል ተግባራችንም ተቀባይነት ማግኘታችንን እንድታረጋግጥልን በማይታዩት ሠራዊቶችህም እንድትደግፈን ለአንተ ለምናበረክተውም አገልግሎት ሽንጦቻችንን እንድታጠናክርልን ለትዕዛዝህ ትሑታን ተገዥዎችና ከአንተም ጋር የምንቋረብ አምላኪ አገልጋዮች እንድታደርገን አንተን በመማፀን ላይ የምንገኝ አገልጋዮችህ ነን፡፡
አቤቱ አንተ ጌታችን ሆይ! እኛ ደካሞች ነን፣ አንተ ደግሞ ኃያሉ፣ ኃይል የተመላው ነህ እኛ ሕይወት አልባዎች ነን፡፡ አንተ ደግሞ ታላቁ ሕይወት ሰጪ መንፈስ ነህ፡፡ እኛ ችግረኞች ነን፡፡ አንተ ደግሞ በሕይወት አኗሪው ኃይል የተመላው ነህ፡፡
አቤቱ አንተ ጌታችን ሆይ! ፊቶቻችንን ምሕረት ወደተመላው ገጽታህ መልስልን፣ ከመንግስተ-ሰማያው የአንተ ገበታ የተትረፈረፈውን የአንተን ፀጋ መግበን በላቁት የአንተ መላእክት ሠራዊት እርዳን፣ በአብሃ መንግስትም ቅዱሳን አማካይነት አጠንክረን፡፡
በእውነቱ አንተ ቸሩ መሐሪው ነህ፡፡ አንተ የታላቅ በረከት ባለቤት ነህ በእርግጥም አንተ ሩኅሩኁና ጸጋ-የተመላው ነህና፣ጸጋ-የተመላው ነህና፡፡
- Bahá'u'lláh