Return to BahaiPrayers.net   Facebook

For the Dead

እርሱ አምላክ ነው፤ እርሱ የፍቅራዊ ደግነትና የቸርነት ጌታ የሆነው የተከበረ ነው፤ አንተ ምንም የማይሳንህ ጌታ የሆንክ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን፣ ምንም የማይሳንህ ስለመሆንህና ስለኃያልነትህ ስለሉዓላዊነትህና ስለፍቅራዊ ደግነትህ፣ ስለፀጋህና ስለሥልጣንህ፣ ስለሕያውነትህ አንድዬነትና ስለህላዌህ አንድነት፣ከፍጥረት ዓለምና በዚያም ከሚገኙት ሁሉ የተቀደስክና የተከበርክ ስለመሆንህ እመሠክራለሁ፡፡

አምላኬ ሆይ! ከአንተ በቀር ከሁሉም ተላቅቄ አንተን አጥብቄ መያዜንና ወደ ቸርነትህ ውቅያኖስ፣ ወደ ልግስናህ ሰማይና ወደ ፀጋህ ቀኑ ኮከብ ዛሬ ታየኛለህ፡፡

ጌታ ሆይ! በአገልጋይህ ውስጥ አደራህን እንዳስቀምጥክና ይህም ለዓለም ህይወት የሰጠህበት መንፈስ መሆኑን እመሰክራለሁ፡፡ በቀናትህ የፈፀመውን ሥራ ምሕረት በተመላበት ሁኔታ እንድትቀበለው በግልፀትህ ሉል ብርሃን እለምንሃለሁ፡፡ በመልካም ፈቃድህ ክብር እንዲጎናፀፍና በአንተ ተቀባይነት እንዲያጌጥ ፈቃድህ ይሁን፡፡

ጌታዬ ሆይ! አቤቱ አንተ የሰዎች ሁሉ ጌታ ሆይ! እኔ ራሴና የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ስለ ኃያልነትህ እንመሰክራለን፤ ይህን ወደ አንተ ወደ መንግስተ ሰማያዊ ስፍራህ፣ ወደ ላቀው ገነትህና ወደ ቅርበትህ ማረፊያ ያረገውን መንፈስ ከአንተ ከራስህ እንዳታገልለው እለምንሃለሁ፡፡

አምላኬ ሆይ፣ አገልጋይህ ብዕር ሊገልፃቸው አንደበትም ሊያወሳቸው በማይችል መንግስተ ሰማያዊ ሥፍራዎች ውስጥ ከሕሩያንህ፣ ከቅዱሳንህና ከመልእክተኞችህ ጋር እንዲወዳጅ ፈቃድህ ይሁን፤

ጌታዬ ሆይ፤ በእውነቱ ምስኪኑ ወደ ሀብትህ መንግስት ባይተዋሩ በክልሎችህ ውስጥ ወዳለው መኖሪያ ቤቱ እርሱ በጣም የተጠማው ወደ በረከትህ መንግስተ ሰማያዊ ወንዝ ገሥግሷል፡፡ ጌታ ሆይ ከፀጋህ ማዕድና ከበረከትህ ችሮታ ድርሻውን አትንፈገው፤ አንተ በእውነቱ ፍጹም ኃያሉ፤ ፀጋ የተመላው ፍጹም በረከት የተመላው ነህና!

አምላኬ ሆይ፣ አደራህ ወደ አንተ ተመልሷል፡፡ አሁን አቀባበል ላደረግህለት እንግዳህ ስጦታዎችህንና ችሮታዎችህን ከፀጋህም ዛፍ ፍሬዎች መለገሱ በምድርና በሰማይ የሚገኙ ግዛቶችህን ከከበበው ፀጋህና በረከትህ የሚጠበቅ ነው፤ አንተ የፈቀድከውን ለማድረግ ሥልጣን አለህ፤ ከአንተ ፀጋ ከተመላው ከሁሉም በላይ በረከት ከተመላው ከሩኅሩኁ ከለጋሱ ከይቅር ባዩ ከክቡሩ ከሁሉን አዋቂው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡

ጌታዬ ሆይ ሰዎች እንግዳቸውን እንዲያከብሩ እንዳዘዝካቸው እርሱ ወደ አንተ ያረገውም በእውነቱ አንተ ዘንድ እንደደረሰና ቅርበትህን እንደተቀዳጀ እመሠክራለሁ፤ እንደፀጋህና እንደቸርነትህ ተቀበለው፣ በክብርህ አገልጋዮችህን ካዘዝካቸው ተግባር ራስህም ወደ ኋላ እንደማትል፣ እርሱን በበረከትህ ገመድ ላይ የተንጠላጠለውንና ወደ ሀብትህ ጎሕ ያረገውን እንደማትነፍገው በእርግጥ አውቃለሁ፡፡

ከአንተ ከአንዱ ከአንደዬው ኃይል ከተመላው፣ ከሁሉን አዋቂው በረከት ከተመላው በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ ጌታ አምላኬ ሆይ፣ ክብር ለአንተ ይሁን! እርሱን በዘላለማዊ ሉዓላዊነትህ ኃይል ያከበርከውን አታዋርደው ወደ ዘለዓለማዊ መቅደስህ እንዲገባ ያደረግኽውንም ከአንተ እንዲርቅ አታድርገው፤ አምላኬ ሆይ፣ እርሱን አንተ በጌትነትህ ጥላ ሥር የከለልከውን ከአንተ መሸሻው የነበርከውን ከአንተ ዘንድ ታባርረዋለህና እርሱን አንተ ከፍ ያደረግኽውን ታዋርደዋለህን. ወይም እርሱን አንተን ለማሰታወስ ያስቻልከውን ትረሳዋለህን?

አንተ የተከበርክ፣ እጅግ በጣም የተከበርክ ነህ! አንተ ከእምቅድመ ዓለም ጀምረህ የመላው ፍጥረት ንጉሥና ዋና አንቀሳቃሹ የነበርከው ነህ፣ ለዘላለምም የተፈጠሩት ነገሮች ሁሉ ጌታና ወሳኛቸው ሆነህ መኖርህን ትቀጥላለህ፤ አምላኬ ሆይ አንተ የተከበርክ ነህ ለአገልጋዮችህ ምሕረት መለገስን ብታቋርጥ ሌላ ማን ምሕረት ያደርግላቸዋል፡፡ አንተ ተወዳጆችህን ካልደረህ ፤ ሌላ ማን ሊራዳቸው ይችላል?

አንተ የተከበርክ፣ ለመገመት ከሚቻል በላይ የተከበርክ ነህ! አንተ ለእውነተኝነትህ የተወደስክ ነህ፤ በአርግጥም እኛ ሁላችንም አንተን እናመልካለን፤ አንተ በፍርድህ ግልጽ ነህ፣በእውነትም እኛ ሁላችንም ለአንተ እንመሠክራለን አንተ በእርግጥ ለፀጋህ የተወደድህ ነህ፤ ከአንተ በአደጋ ጊዜ ረዳቱ፣ በገዛ ራሱ ነዋሪ ከሆንከው በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡

አምላኬ ሆይ! አቤቱ አንተ ኃጢአትን ይቅር ባዩ ስጦታዎች ሰጪው ጭንቅንም አትፊው ሆይ! በእውነቱ ሥጋዊ ልብስን ጥለው ወደ መንፈሳዊው ዓለም ያረጉትን ሁሉ ኃጢአት ይቅር ትልላቸው ዘንድ እማፀንሃለሁ፡፡

ጌታዬ ሆይ ከኃጢአት ሁሉ አንፃቸው ኃዘናቸውን አስወግድላቸው፣ ጨለማውንም ወደ ብርሃን ለውጥላቸው፤ ወደ ተድላ ገነት እንዲገቡ አድርጋቸው ፍጹም ንጹህ በሆነው ውሃ እጠባቸው፤ ከሁሉም በላይ ከፍተኛ በሆነው ተራራ ላይ ያለውን ግርማህንም እንዲያዩ አድርጋቸው፤

 


English  
ភាសាខ្មែរ  
አማርኛ.  
Afrikaans  
Alaska Native  
American Indian  
Azərbaycan  
Bahasa Indonesia  
Bahasa Malaysia  
Bidayuh  
Bosanski  
Canadian Indigenous  
Català  
Cebuano  
Česky  
Chamorro  
Chichewa  
Corsica  
Cymraeg  
Daga  
Dansk  
Deutsch  
Dzongkha  
Eesti  
Español  
Esperanto  
Euskara  
Fiji  
Filipino  
Føroyar  
Français  
Frysk  
Hausa  
Hawaiian  
Hiri Motu  
Hrvatski  
Irish  
Íslenska  
Italiano  
Kabyle  
Kalaallisut  
Kiribati  
Kiswahili  
Kreyol Ayisyen  
Kuanua  
Kube  
Latviešu  
Lëtzebuergesch  
Lietuvių  
Luganda  
Magyar  
Malagasy  
Malti  
Māori  
Marshallese  
Melpa  
Montenegrin  
Nalik  
Namibia  
Nederlands  
Norsk  
Papiamentu  
Polski  
Português (BR)  
România  
Sámi  
Samoan  
Sarawak  
Sesotho  
Shqip  
Slovenščina  
Slovensky  
Sranan Tongo  
Srpski српски  
Suomi  
Svenska  
Tetum  
Tiếng Việt  
Tok Pisin  
Tongan  
Türkçe  
Türkmençe  
Tuvalu  
Vanuatu  
ελληνικά  
Беларускі  
български  
Кыргыз  
Монгол хэл  
Русский  
Тоҷикӣ  
Україна  
հայերեն  
اُردُو  
العربية  
فارسی  
नेपाली  
मराठी  
हिंदी  
বাংলা  
ગુજરાતી  
ଓଡ଼ିଆ  
தமிழ்  
తెలుగు  
ಕನ್ನಡ  
മലയാളം  
ภาษาไทย  
ພາສາລາວ  
한국어  
日本語  
简体中文  
繁體中文  
Windows / Mac